የጥራት መንድር አመራርና ሠራተኞች 18ኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን አከበሩ፡፡
አዲስ አበባ፡ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (ኢሥኢ)
የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ የጥራት መንደር የስራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተገኙበት በውቡ የጥራት መንደር ቅጥር ግቢ ውስጥ "ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!" በሚል መሪ ቃል 18ኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን በዓል አክብረዋል፡፡