Skip to main content

የጥራት መንድር አመራርና ሠራተኞች 18ኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን አከበሩ፡፡

አዲስ አበባ፡ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (ኢሥኢ) የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩትን ጨምሮ የጥራት መንደር የስራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተገኙበት በውቡ የጥራት መንደር ቅጥር ግቢ ውስጥ "ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!" በሚል መሪ ቃል 18ኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን በዓል አክብረዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ የመጀመሪያውን ሩብ ዓመት ሪፖርት ገመገመ፡፡

አዲስ አበባ፡ መስከረም 27/2018 ዓ.ም (ኢሥኢ) የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት በ2018 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ተግባራትን አፈፀፃም በዛሬው ዕለት ገምግሟል፡፡

ጥራትን ማስጠበቅ የሀገራችን ዋና ማጠንጠኛ ነጥብ መሆኑ ተጠቆመ፡፡

አዲስ አበባ፡ ነሐሴ 27/12/2017 ዓ.ም (ኢሥኢ) የኢትዮጵያን ይግዙ በሚል መርህ ከተከፈተው የንግድ ሳምንት ጎን ለጎን ሁለተኛው ዙር የፓናል ውይይት ዛሬም በምርትና አገልግሎት ጥራት ማስጠበቅ ላይ ትኩረት በማድረግ በውቡ የጥራት መንደር ግቢ በኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት አዳራሽ ተካሂዷል፡፡

የሀገርን ምርት መጠቀም በራስ ከመተማመን ባለፈ የሀገርንም ኢኮኖሚ በማሳደግ ረገድ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፡ ነሀሴ 26/2017 ዓ.ም (ኢሥኢ) የኢትዮጵያን ይግዙ በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ከሚገኘው የንግድ ሳምንት ኤክስፖ አካል የሆነ የሃገር ውስጥ ንግድ ፓናል ውይይት በግዙፉ የጥራት መንደር ግቢ ውስጥ በኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡

ፕሬዝዳንቱ "የኢትዮጵያን ይግዙ" በሚል መሪቃል የተዘጋጀውን የንግድ ሳምንት በይፋ ከፈቱ፡፡

አዲስ አበባ፡ ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (ኢሥኢ) የኤፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ታዬ አፅቀስላሴ በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አዘጋጅነት "የኢትዮጵያን ይግዙ" በሚል መሪ ቃል ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ዓመታዊ የንግድ ሳምንት ኤግዚቢሽንና ባዛር በዛሬው ዕለት በይፋ ከፍተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ፡፡

አዲስ አበባ፡ ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም (ኢሥኢ) ኢትዮጵያ ባዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ የሚታደሙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተወካዮች የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩትን ጎብኝተዋል።