አስራ ዘጠነኛው የአፍሪካ ሥነ-ልክ ድርጅት /AFRIMETS/ ጠቅላላ ጉባዔ በስኬት ተጠናቀቀ፡፡
አዲስ አበባ፡ ነሐሴ 2018 ዓ.ም (ኢሥኢ)
በኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ለተከታታይ አምስት ቀናት "ሥነ-ልክ ለዲጅታል ሽግግር ተዓማኒ ልኬቶች ለአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፋንታ" በሚል መሪ ሀሳብ በጥራት መንደር ሲካሄድ የቆየው 19ኛው የአፍሪካ ሥነ-ልክ ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ በስኬት ተጠናቋል፡፡







