Skip to main content

PAQI Policy Council Delegation Conducts Strategic Visit to EMI

Addis Ababa, Ethiopia 05 March 2025 (EMI). A high-level delegation from the Pan African Quality Infrastructure (PAQI) Policy Council visited the Ethiopian Metrology Institute (EMI).

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ ዛሬ ብሔራዊ የጥራት መንደርን መረቁ::

ህዳር 14/2017 ዓ.ም - ኢ.ስ.ኢ በአፍሪከ ደረጃ በአይነቱና በሚሰጠው አገልግሎት ልዩ የሆነና የተለያዩ የጥራት መሠረተ ልማቶችን አንድ አካቶ የያዘው ብሔራዊጥራት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ተመርቋል።

የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሠራተኞች የበዓል ስጦታ አበረከተ፡፡

አዲስ አበባ ጳጉሜ 4 ቀን 2016 ዓ.ም /ኢስኢ/ የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር በሰጡት አቅጣጫ መሰረት አዲስ ዓመትንና ጳጉሜ 4 "የህብር ቀን" ምክንያት በማድረግ አነስተኛ ገቢ ላላቸው አርባ ለሚሆኑ የተቋሙ ሠራተኞች ለበዓል መዋያ የሚሆን ዘይትና ዱቄት በስጦታ አበርክቷል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ለግንባር ቀደም ሠራተኞች የዕውቅናና ሽልማት ሥነ-ስርዓት አካሄደ፡፡

ነሐሴ 21/2016 ዓ.ም /ኢስኢ/ የኢትዮጵያን ይግዙ በሚል መሪ ቃል ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከነሐሴ 19-23/2016 ዓ.ም ያዘጋጀውን የንግድ ሳምንት ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት በ2016 በጀት ዓመት የጎላ አስተዋፅዖ ላበረከቱ ምስጉን ሠራተኞች የዕውቅናና ሽልማት ሥነ-ስርዓት አካሂዷል፡፡

የኢትዮጵያን ምርትና አገልግሎት መግዛት ዕድገትን ለማፋጠን ያግዛል ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፡ ነሐሴ 19/2016 ዓ.ም /የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያን ምርትና አገልግሎት መግዛት የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባሻገር የግሉን የንግድ ዘርፍ ያበረታታል፣ የሀገርንም ዕድገት ያፋጥናል ሲሉ "የኢትዮጵያን ይግዙ" በሚል መሪ ቃል በተከፈተው

"የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ተካሄደ፡፡

ነሐሴ 17-2016 ዓ.ም ኢስኢ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች "የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ" በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት እንጦጦ ፓርክ አካባቢ በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡

17ኛውን የአፍሪካ አህጉር የሥነ-ልክ ተቋም ስብሰባ የሚካፈል ልዑክ ወደ ኬንያ ማምራቱ ተገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም (ኢስኢ) 17ኛውን የአፍሪካ አህጉር የሥነ-ልክ ተቋም ስብሰባ ለመካፈል በኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍቅረዓብ ማርቆስ የተመራ ልዑክ በዛሬው እለት ከአቻ የሥነ-ልክ ተቋም አመራሮች እና ቴክኒካል ኮሚቴዎች ጋር በጋራ እና በአህጉር አቀፍ የሥነ-ልክ ጉዳዮች ላይ በናይሮቢ ኬንያ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል።

የኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ሠራተኞች በ2017 በጀት ዕቅድ እና በጊዜ አጠቃቀም ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24/2016 ዓ.ም (ኢስኢ) የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሠራተኞች በ2017 በጀት ዕቅድ፣ በጊዜ አጠቃቀም፣ መልካም ሥነ-ምግባር እና ለጥናትና ምርምር የተቋሙን ነባራዊ ሁኔታ በማስመልከት በአዳማ ከተማ ውይይት አድርገዋል፤የአዳማ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪንም ጉብኝተዋል፡፡

የሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና የኢኖቬሽን አውደ ርዕይ በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20/2016 ዓ.ም (ኢስኢ) የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ከአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት እና ከሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት አምራች ማህበራት ጋር በመተባበር ከሰኔ 15-20/2016 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ አውደርዕይ በሚሊኒየም አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል፡፡

ኢንስቲትዩቱ “ለተሻለ ነገ ዛሬ እንለካለን” በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፉን የሥነ-ልክ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች አከበረ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2016 ዓ.ም (ኢስኢ) የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም አቀፉን የሥነ-ልክ ቀን “ለተሻለ ነገ ዛሬ እንለካለን” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል፡፡
Subscribe to News